Friday, March 20, 2026

About the Ethiopian Civil Society Organizations Council (ECSOC)

The Ethiopian Civil Society Organizations Council (ECSOC) is an independent apex body legally representing the civil society sector, which consists of organizations, consortia, associations, forums, and networks. ECSOC was established on December 31, 2020, by the 300 General Assembly members that consisted of CSO representatives and are the founders of the Council.

The Council was formed as per Article 85 of the Civil Society Organizations’ Proclamation 1113/2019, which stipulates that the establishment of a Council shall be governed by the full participation of “all” CSOs in Ethiopia and, further, that the Council shall “represent and coordinate the civil society sector”. This implies that ECSOC represents all CSOs in Ethiopia.

Sponsors of 5th CSOs Week

 

 
አመታዊውን የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሳምንት ዘንድሮም በደማቅ ሁኔታ ለአምስተኛ ጊዜ ማክበር ተጀምሯል። የዘንድሮን የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሳምንት የኢፌዲሪ ሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን እና የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት በጋራ ያዘጋጁት ሲሆን ”ራስን መቻል ለዘላቂ ሰላም እና ለአካታች ልማት” በሚል መሪ ቃል በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር ለ3 ተክታታይ ቀናቶች ይከናወናል።
በዝግጅቱ ከባለፈው አመት በተሸለ ከ115 በላይ ድርጅቶች ስራዎቻቸውን በኤግዝቢሽን ለህዝብ ይፋ ከማድረግ አልፎ፣ የልማት አጋሮች፣ የግሉ ዘርፍ፣ የመንግስት ተቋማት እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላቶችን የሚያሳትፉ 7 የፓናል ውይይት መድረኮች ይከናወናሉ።
በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ “መንግሥት ከለውጡ ማግስት ጀምሮ ለሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው.” ብለዋል።
በመክፈቻ ንግግራቸው የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ፕሬዝደንት አቶ አህመድ ሁሴን “ድርጅቶች የመደራጀት መብታቸውን በመጠቀም በልማት፣ በዴሞክራሲ እና በሰላም ግንባታ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው” ብለዋል።
በቀጣዮቹ ሁለት ቀናቶች (የካቲት 27 እና የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም.) በፓናል ውይይቶቹ የሚነሱ ርዕሰ ሃሳቦች በሰላም ግንባታ እና በመልካም አስተዳደር፣ በዲጂታል ሚዲያ፣ በስርዓተ ጾታ፣ በኢትዮጵያ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ጾታን መሰረት ያደረገ ጥቃ፣ በሰብአዊ ድጋፍ እንዲሁም ጠቅላላ ምርጫ እና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሚና ላይ ውይይቶች ይደረጋሉ።
የፍትሕ ሚኒስትር ሃና አርዓያሥላሴ ``ጠንካራ ኢትዮጵያን ለመገንባት በቅንጅት እና በመናበብ መሥራት የሁሉም ድርሻ ነው`` ብለዋል።
የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሳምሶን ቢራቱ ``ሳምንቱ በባለድርሻ አካላት መካከል ጠንካራ ትስስር እና የልምድ ልውውጥ እንዲኖር ግብዓት እየኾነ መምጣቱን ገልጸዋል።”
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሳምንት ዋነኛ አላማ በዘርፉ ያሉ ድርጅቶች በማህበረሰቡ ውስጥ በሚደረጉ ማናቸውም እንቅስቃሴ ያላቸውን ሚና ለህዝብ እና ለባለድርሻ አካላት እንዲያስተዋውቁ ዕድሉን መፍጠር እና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ከመንግስት፣ ከግሉ ዘርፍ እና ከሌሎች የልማት አጋሮች ጋር ተቀራርበው በትስስር የሚሰሩበትን መድረክን ማመቻቸት ነው።
በዘንድሮው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች 115 የሲቪል ማህበረአሰብ ድርጅቶች ስራቸውን ለህዝብ የሚያሳዩበት ይህ አመታዊ መርሃ ግብር የዘርፉን የገጽታ ግንባታ እንቅስቃሴ የበለጠ ከማጉላቱ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጾ ይኖረዋል፡፡

ECSOC News

5ኛው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሳምንት በይፋ ተጀመረ

0
አመታዊውን የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሳምንት ዘንድሮም በደማቅ ሁኔታ ለአምስተኛ ጊዜ ማክበር ተጀምሯል። የዘንድሮን የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሳምንት የኢፌዲሪ ሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን እና የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት በጋራ ያዘጋጁት ሲሆን ”ራስን መቻል ለዘላቂ ሰላም እና...
Read More...

Consultative meeting on CSO proclamation 1113/2019 draft amendment ECSOC and PDN

0
የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት እና ፕሮ ዴቨሎፕመንት ኔትዎርክ በጋራ ባዘጋጁት የግማሽ ቀን የምክክር አውደ ጥናት በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር በቀረቡ በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች አዋጅ 1113/2019 ማሻሻያ ሃሳቦች ላይ ያተኮረ ውይይት ተደረገ። ስብሰባው እነዚህ ማሻሻያዎች በተወሰኑ የትኩረት...
Read More...

Tree Planting 2025

0
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት አደጋዎች እንዳይከሰቱ አስቀድሞ ከመከላከል እንዲሁም አደጋዎች ሲገጥሙ ደግሞ ሰብአዊነትን መሰረት ያደረገ አፋጣኝ ምላሽ በመስጠት ከመንግስት ተቋማት ጋር በመሆን የረዥም ጊዜ ሥራ ሲሰሩ መቆየታቸው ታሪክ የሚዘክረው ነው። ማክሰኞ ሀምሌ 8 ቀን 2017 ዓ.ም...
Read More...

Quarterly panel discussion CSO National Dialogue Reference Group and Ethiopian National Dialogue Commission

0
#LastWeekHighlights The impact continues! Here's a recap of the discussions and connections made at our event on July 10th where a quarterly panel discussion among CSO national dialogue reference...
Read More...